• ”ሑሩ ወመሐሩ ውስተ ኩሉ አጽናፈ ዓለም ” ማቴ 28፤19

  • ከታሪክ ማኅደር

  • ከታሪክ ማኅደር፦ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ አቴና ግሪክ ትምህርት ቤት በነበሩበት ወቅት

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን

የኖርዲክ እና ግሪክ ሀገረ ስብከት – ስቶክሆልም

ልዩ የወላጆች ስልጠና ተጀመረ፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የኖርዲክ እና ግሪክ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ለ8 ሳምንታት የሚቆየው “ዘመኑን የዋጀ ተተኪ ኦርቶዶክሳዊ ተዋሕዶ ትውልድ መፍጠር” በሚል መሪ ቃል ለወላጆች የተዘጋጀው ስልጠና ሰኞ የካቲት 17 ቀን 2017 ዓም ተጀምሯል። በመጀመሪያው ቀን ከ325 በላይ ቤተሰቦች የተሳተፉ ሲሆን፣ ከሀገረ ስብከቱ ውጪም በተለያዩ የአውሮፓ አገሮች የሚኖሩ ወላጆች ጭምር የተሳተፉበት ስልጠና እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።

በኖርዌይ ስታቫንገር ከተማ አዲስ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ተገዝቶ ተባረከ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በኖርዲክና ግሪክ ሀገረ ስብከት በኖርዌይ ስታቫንገር ከተማ የደብረ ገነት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ተገዝቶ የካቲት ፲፭ እና ፲፮/ ፳፻፲፯ ዓ/ም የኖርዲክና ግሪክ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ መልአከ አሚን ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ፣ ከተለያዩ ሀገሮች የመጡ ሊቃውንት እና ምእመናን በተገኙበት በብፁዕ አቡነ ኤልያስ የኖርዲክና ግሪክ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ተባርኳል።

በኖርዌይ በርገን ከተማ አዲስ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ተገዝቶ ተባረከ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በኖርዲክና ግሪክ ሀገረ ስብከት በኖርዌይ በርገን ከተማ የመንበረ ልዑል ቅዱስ ሚካኤል ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ተገዝቶ የካቲት ፰ እና ፱ / ፳፻፲፯ ዓ/ም የኖርዲክና ግሪክ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ መልአከ አሚን ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ፣ ከተለያዩ ሀገሮች የመጡ ሊቃውንት እና ምእመናን በተገኙበት፣ በብፁዕ አቡነ ኤልያስ የኖርዲክና ግሪክ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ተባርኳል።

ብጹእ አቡነ ኤልያስ

የኖርዲክ እና ግሪክ ሀገረ ስብከት – ስቶክሆልም ሊቀ ጳጳስ

በፌስቡክ ያግኙን

የሀገረ ስብከቱ አዲሱ የባንከ ቁጥር

Plusgiro፡ 1866938-2
IBAN: SE 28950000996042 186 6938-2
Swift code/BIC: NDEASESS

የዝክረ ነዳያን ባንክ  ቁጥር:

Plusgiro 78 62 90-7
IBAN፡ SE 1795000099604207862907

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን

የኖርዲክ እና ግሪክ ሀገረ ስብከት – ስቶክሆልም

  • 08-7492928 / 707302826
  • 427, 12404 Bandhagen, Sweden