በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
08-7492928 / 707302826
የሀገረ ስብከቱ አዲሱ የባንከ ቁጥር
Plusgiro፡ 1866938-2
IBAN: SE 28950000996042 186 6938-2
Swift code/BIC: NDEASESS
የዝክረ ነዳያን ባንክ ቁጥር:
Plusgiro 78 62 90-7
IBAN፡ SE 1795000099604207862907
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
ልዩ የወላጆች ስልጠና ተጀመረ፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የኖርዲክ እና ግሪክ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ለ8 ሳምንታት የሚቆየው “ዘመኑን የዋጀ ተተኪ ኦርቶዶክሳዊ ተዋሕዶ ትውልድ መፍጠር” በሚል መሪ ቃል ለወላጆች የተዘጋጀው ስልጠና ሰኞ የካቲት 17 ቀን 2017 ዓም ተጀምሯል። በመጀመሪያው ቀን ከ325 በላይ ቤተሰቦች የተሳተፉ ሲሆን፣ ከሀገረ ስብከቱ ውጪም በተለያዩ የአውሮፓ አገሮች የሚኖሩ ወላጆች ጭምር የተሳተፉበት ስልጠና እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።
በኖርዌይ ስታቫንገር ከተማ አዲስ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ተገዝቶ ተባረከ።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በኖርዲክና ግሪክ ሀገረ ስብከት በኖርዌይ ስታቫንገር ከተማ የደብረ ገነት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ተገዝቶ የካቲት ፲፭ እና ፲፮/ ፳፻፲፯ ዓ/ም የኖርዲክና ግሪክ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ መልአከ አሚን ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ፣ ከተለያዩ ሀገሮች የመጡ ሊቃውንት እና ምእመናን በተገኙበት በብፁዕ አቡነ ኤልያስ የኖርዲክና ግሪክ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ተባርኳል።
በኖርዌይ በርገን ከተማ አዲስ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ተገዝቶ ተባረከ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በኖርዲክና ግሪክ ሀገረ ስብከት በኖርዌይ በርገን ከተማ የመንበረ ልዑል ቅዱስ ሚካኤል ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ተገዝቶ የካቲት ፰ እና ፱ / ፳፻፲፯ ዓ/ም የኖርዲክና ግሪክ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ መልአከ አሚን ቀሲስ ለማ በሱፍቃድ፣ ከተለያዩ ሀገሮች የመጡ ሊቃውንት እና ምእመናን በተገኙበት፣ በብፁዕ አቡነ ኤልያስ የኖርዲክና ግሪክ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ተባርኳል።